ሱረቱ Al-Qalam القلم
52 አንቀጾች · መካ · የወረደበት ቅደም ተከተል 2
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ نٓ وَٱلْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَ
Amharic Translation - Africa Academy1. ኑን፤ በብዕር እና በዚያም በሱ በሚጽፉት ሁሉ እምላለሁ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
مَآ أَنتَ بِنِعْمَةِ رَبِّكَ بِمَجْنُونٍ
Amharic Translation - Africa Academy2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አንተ በጌታህ ጸጋ ምክኒያት ዕብድ አይደለህም::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَإِنَّ لَكَ لَأَجْرًا غَيْرَ مَمْنُونٍ
Amharic Translation - Africa Academy3. ላንተም ከጌታህ የማይቋረጥ ምንዳ (የልፋት ዋጋ) በእርግጥ አለህ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٍ
Amharic Translation - Africa Academy4. አንተም በታላቅ ጸባይ ላይ ነህ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَسَتُبْصِرُ وَيُبْصِرُونَ
Amharic Translation - Africa Academy5. ወደ ፊት አንተም ታያለህ፤ እነርሱም ያያሉ፤
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
بِأَييِّكُمُ ٱلْمَفْتُونُ
Amharic Translation - Africa Academy6. ዕብደት በማንኛችሁ እንዳለ (እብዱ ማን እንደሆነ)::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعْلَمُ بِٱلْمُهْتَدِينَ
Amharic Translation - Africa Academy7. ጌታህ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው አዋቂ ነው። ወደ ቀናው መንገድ ተመሪዎችንም አዋቂ ነው::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَلَا تُطِعِ ٱلْمُكَذِّبِينَ
Amharic Translation - Africa Academy8. ስለዚህ ለአስተባባዩች (ሁሉ) አትታዘዝ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَدُّوا۟ لَوْ تُدْهِنُ فَيُدْهِنُونَ
Amharic Translation - Africa Academy9. (አስተባባዩች) ብትመሳሰላቸውና እነርሱም ቢመሳሰሉህ ተመኙ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَلَا تُطِعْ كُلَّ حَلَّافٍ مَّهِينٍ
Amharic Translation - Africa Academy10. መሓለኛን ወራዳን ሁሉ አትታዘዝ።
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
هَمَّازٍ مَّشَّآءٍۭ بِنَمِيمٍ
Amharic Translation - Africa Academy11. ሰውን አነዋሪን፤ ነገር አሳባቂን፤
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
مَّنَّاعٍ لِّلْخَيْرِ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ
Amharic Translation - Africa Academy12.ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፤ ወሰን አላፊን፤ ኃጢአተኛንም፤
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
عُتُلٍّۭ بَعْدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ
Amharic Translation - Africa Academy13. ልበ ደረቅን ከዚህ ሁሉ በተጨማሪ የዝሙት ልጅ ዲቃላን (አትታዘዝ)::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَن كَانَ ذَا مَالٍ وَبَنِينَ
Amharic Translation - Africa Academy14. የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመሆኑ (ያስተባብላል)።
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلْأَوَّلِينَ
Amharic Translation - Africa Academy15. በእርሱ ላይ እንቀፆቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
سَنَسِمُهُۥ عَلَى ٱلْخُرْطُومِ
Amharic Translation - Africa Academy16. በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክትን እናደርግበታለን::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
إِنَّا بَلَوْنَٰهُمْ كَمَا بَلَوْنَآ أَصْحَٰبَ ٱلْجَنَّةِ إِذْ أَقْسَمُوا۟ لَيَصْرِمُنَّهَا مُصْبِحِينَ
Amharic Translation - Africa Academy17. እኛ እነዚያን የአትክልቲቱን ባለቤቶች ማልደው ፍሬዋን ሊለቅሟት (አላህ ቢሻ ሳይሉ) በማሉ ጊዜ እንደሞከርን ሁሉ የመካ ሰዎችንም ሞከርናቸው::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَلَا يَسْتَثْنُونَ
Amharic Translation - Africa Academy18. (በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَطَافَ عَلَيْهَا طَآئِفٌ مِّن رَّبِّكَ وَهُمْ نَآئِمُونَ
Amharic Translation - Africa Academy19.እነርሱ የተኙ ሆነዉም ሳሉ ከጌታህ የሆነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَأَصْبَحَتْ كَٱلصَّرِيمِ
Amharic Translation - Africa Academy20. እንደ ሌሊት ጨለማ የከሰለች ሆና አነጋች (አደረች)።
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَتَنَادَوْا۟ مُصْبِحِينَ
Amharic Translation - Africa Academy21.ያነጉም ሆነው ተጠራሩ
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَنِ ٱغْدُوا۟ عَلَىٰ حَرْثِكُمْ إِن كُنتُمْ صَٰرِمِينَ
Amharic Translation - Africa Academy22. "ቆራጮች እንደ ሆናችሁ ወደ እርሻችሁ ለመሄድ ማልዱ በማለት" (ተጠራሩ)::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَٱنطَلَقُوا۟ وَهُمْ يَتَخَٰفَتُونَ
Amharic Translation - Africa Academy23. እነርሱ የሚያሾካሾኩ ሆነው ሄዱም::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَن لَّا يَدْخُلَنَّهَا ٱلْيَوْمَ عَلَيْكُم مِّسْكِينٌ
Amharic Translation - Africa Academy24. ዛሬ በእናንተ ላይ አንድም ድሃ እንዳይገባት በማለትና
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَغَدَوْا۟ عَلَىٰ حَرْدٍ قَٰدِرِينَ
Amharic Translation - Africa Academy25. ድሆችን በመከልከልም ላይ በሀሳባቸው ቻዮች ሆነው ማለዱ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَلَمَّا رَأَوْهَا قَالُوٓا۟ إِنَّا لَضَآلُّونَ
Amharic Translation - Africa Academy26. ከዚያ ተቃጥላ ባዩዋት ጊዜ (እንዲህ) አሉ: «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን፤
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
بَلْ نَحْنُ مَحْرُومُونَ
Amharic Translation - Africa Academy27. «ይልቁንም እኛ ከአላህ የተከለከልን እደለ ቢሶች ነን» አሉ።
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
قَالَ أَوْسَطُهُمْ أَلَمْ أَقُل لَّكُمْ لَوْلَا تُسَبِّحُونَ
Amharic Translation - Africa Academy28. (ከመካከላቸው) ትክክለኛቸው (አስተዋያቸው)፡- «እናንተ አላህን ለምን አታጠሩም (አታወሱም) አላልኳችሁም ነበርን?» አለ።
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
قَالُوا۟ سُبْحَٰنَ رَبِّنَآ إِنَّا كُنَّا ظَٰلِمِينَ
Amharic Translation - Africa Academy29. «(ሁላቸዉም) ጌታችን ጥራት ይገባው፤ እኛ በዳዩች ነበርን» አሉ።
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ يَتَلَٰوَمُونَ
Amharic Translation - Africa Academy30. እርስ በራሳቸው የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
قَالُوا۟ يَٰوَيْلَنَآ إِنَّا كُنَّا طَٰغِينَ
Amharic Translation - Africa Academy31. «ዋ፤ጥፋታችን፤ እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን» አሉ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
عَسَىٰ رَبُّنَآ أَن يُبْدِلَنَا خَيْرًا مِّنْهَآ إِنَّآ إِلَىٰ رَبِّنَا رَٰغِبُونَ
Amharic Translation - Africa Academy32. «ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል:: እኛ ወደ ጌታችን ከጃዩች ነን» አሉ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
كَذَٰلِكَ ٱلْعَذَابُ وَلَعَذَابُ ٱلْـَٔاخِرَةِ أَكْبَرُ لَوْ كَانُوا۟ يَعْلَمُونَ
Amharic Translation - Africa Academy33. (የአላህ) ቅጣቱ ልክ እንደዚሁ ነው:: የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ከዚህ የበለጠ ከባድ ነው:: የሚያውቁ ቢሆኑ ኖሮ (ከዚህ ቅጣት በተጠነቀቁ ነበር)::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ عِندَ رَبِّهِمْ جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
Amharic Translation - Africa Academy34. ለጥንቁቆች በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَفَنَجْعَلُ ٱلْمُسْلِمِينَ كَٱلْمُجْرِمِينَ
Amharic Translation - Africa Academy35. ሙስሊሞችን እንደ ከሓዲያን እናደርጋለን? (አናደርግም)::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ
Amharic Translation - Africa Academy36. ለእናንተ ምን (አስረጂ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ( ምን ነካችሁ)::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَمْ لَكُمْ كِتَٰبٌ فِيهِ تَدْرُسُونَ
Amharic Translation - Africa Academy37. በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
إِنَّ لَكُمْ فِيهِ لَمَا تَخَيَّرُونَ
Amharic Translation - Africa Academy38. በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁን? (የሚል)::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَمْ لَكُمْ أَيْمَٰنٌ عَلَيْنَا بَٰلِغَةٌ إِلَىٰ يَوْمِ ٱلْقِيَٰمَةِ إِنَّ لَكُمْ لَمَا تَحْكُمُونَ
Amharic Translation - Africa Academy39. ወይስ «ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ» በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሳኤ ቀን ደራሽ የሆኑ መሐላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
سَلْهُمْ أَيُّهُم بِذَٰلِكَ زَعِيمٌ
Amharic Translation - Africa Academy40. በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَمْ لَهُمْ شُرَكَآءُ فَلْيَأْتُوا۟ بِشُرَكَآئِهِمْ إِن كَانُوا۟ صَٰدِقِينَ
Amharic Translation - Africa Academy41. ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) ተጋሪዎች አሏቸውን? እውነተኞችም እንደሆኑ ተጋሪዎቻቸውን ያምጡ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
يَوْمَ يُكْشَفُ عَن سَاقٍ وَيُدْعَوْنَ إِلَى ٱلسُّجُودِ فَلَا يَسْتَطِيعُونَ
Amharic Translation - Africa Academy42. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ያን ባት የሚገለጥበትን፤ (ከሓዲያን) ወደ መስገድ የሚጠሩበትና የማይችሉበትን ቀን (አስታውስ)::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
خَٰشِعَةً أَبْصَٰرُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ وَقَدْ كَانُوا۟ يُدْعَوْنَ إِلَى ٱلسُّجُودِ وَهُمْ سَٰلِمُونَ
Amharic Translation - Africa Academy43. ዓይኖቻቸው የፈሩ፤ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲሆኑ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን):: እነርሱ (በምድረ ዓለም) ደህና ሆነው ሳሉ ወደ ስግድት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَذَرْنِى وَمَن يُكَذِّبُ بِهَٰذَا ٱلْحَدِيثِ سَنَسْتَدْرِجُهُم مِّنْ حَيْثُ لَا يَعْلَمُونَ
Amharic Translation - Africa Academy44. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በመሆኑም እኔን በዚህ ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተወኝ፤ (ለእነርሱ እኔ እበቃሃለሁ):: ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَأُمْلِى لَهُمْ إِنَّ كَيْدِى مَتِينٌ
Amharic Translation - Africa Academy45. እነርሱንም አዘገያቸዋለሁ:: (ዘዴዬ) ብቀላየ ብርቱ ነውና::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَمْ تَسْـَٔلُهُمْ أَجْرًا فَهُم مِّن مَّغْرَمٍ مُّثْقَلُونَ
Amharic Translation - Africa Academy46. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ወይንስ በእውነቱ (በማስተማርህ) ዋጋን እንዲከፍሉህ ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
أَمْ عِندَهُمُ ٱلْغَيْبُ فَهُمْ يَكْتُبُونَ
Amharic Translation - Africa Academy47. ወይስ ከእነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር እውቀት አለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَٱصْبِرْ لِحُكْمِ رَبِّكَ وَلَا تَكُن كَصَاحِبِ ٱلْحُوتِ إِذْ نَادَىٰ وَهُوَ مَكْظُومٌ
Amharic Translation - Africa Academy48. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ)፤ ለጌታህ (ዉሳኔ) ፍርድ ታገስ:: (በመበሳጨትና ባለ መታገስ) እንደ ዓሳው ባለቤት እንደ (ነብዩ ዩኑስ) አትሁን:: እርሱ በጭንቀት የተሞላ ሆኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
لَّوْلَآ أَن تَدَٰرَكَهُۥ نِعْمَةٌ مِّن رَّبِّهِۦ لَنُبِذَ بِٱلْعَرَآءِ وَهُوَ مَذْمُومٌ
Amharic Translation - Africa Academy49. ከጌታው የሆነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ሆኖ በተጣለ ነበር::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
فَٱجْتَبَٰهُ رَبُّهُۥ فَجَعَلَهُۥ مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
Amharic Translation - Africa Academy50. ጌታዉም (በነብይነት) መረጠው:: ከደጋጎችም አደረገው::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَإِن يَكَادُ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ لَيُزْلِقُونَكَ بِأَبْصَٰرِهِمْ لَمَّا سَمِعُوا۟ ٱلذِّكْرَ وَيَقُولُونَ إِنَّهُۥ لَمَجْنُونٌ
Amharic Translation - Africa Academy51. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነሆ እነዚያ በአላህ የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው (ሊያጠፉህ) ይቃረባሉ፤ «እርሱም በእርግጥ እብድ ነዉም» ይላሉ::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
وَمَا هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَٰلَمِينَ
Amharic Translation - Africa Academy52.እርሱ ግን ለዓለማት መገሰጫ (ገሳጭ) እንጂ ሌላ አይደለም::
የዚህን አንቀጽ ሁሉንም ትርጉሞች ይመልከቱ →
ርዕስ እየፈለጉ ነው? የትርጉም ፍለጋን ይሞክሩ — ጥያቄዎ በ6,236 አንቀጾች ውስጥ ይፈለጋል።
→