وَإِذْ قُلْنَا ٱدْخُلُوا۟ هَٰذِهِ ٱلْقَرْيَةَ فَكُلُوا۟ مِنْهَا حَيْثُ شِئْتُمْ رَغَدًا وَٱدْخُلُوا۟ ٱلْبَابَ سُجَّدًا وَقُولُوا۟ حِطَّةٌ نَّغْفِرْ لَكُمْ خَطَٰيَٰكُمْ وَسَنَزِيدُ ٱلْمُحْسِنِينَ
Amharic Translation - Africa Academy58. (የኢስራኢል ልጆች ሆይ!) «ወደዚህች ከተማ ግቡ። ከእርሷም ከፈለጋችሁት ስፍራ የፈለጋችሁት መልኩ ተመገቡ:: በሩንም አጎንበሳችሁ ግቡ:: ‹ጥያቄያችንም የኃጢአቶቻችን መሰረዝ ነው።› በሉ:: ኃጢአቶቻችሁን እንምራለን ለበጎ ሰሪዎችም ምንዳ እንጨምርላቸዋለን።» ባልን ጊዜ የሆነውን አስታውሱ።
Amharic Translation - Muhammad Sadiq«ይህችንም ከተማ ግቡ፡፡ ከርሷም በሻችሁት ስፍራ ሰፊን (ምግብ) ተመገቡ፡፡ በሩንም ያጎነበሳችሁ ኾናችሁ ግቡ፤ (ጥያቄያችን የኃጢአታችን መርገፍ ነው) በሉም፡፡ ኃጢአቶቻችሁን ለናንተ እንምራለንና፡፡ በጎ ሠሪዎችንም (ምንዳን) እንጨምርላቸዋለን» ባልን ጊዜ (አስታውሱ)፡፡